22 ተኛው ዓመታዊ ጉባኤ – የዕለተ አርብ

በኢ/ኦተ/ቤ/ክ በሰሜን አሜሪካ አኅጉረ ስብከት የሰንበት ትቤቶች አንድነት ጉባኤ

22 ተኛው ዓመታዊ ጉባኤ በርእሰ አድባራት ጽርሐ አርያም ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል አርብ ነሔሴ 27 ከምሽቱ 6:00 pm ተጀመረ።

የደብሩ (የካቴድራሉ) አስተዳዳሪ መልአከ አርያም አባ ኃይለ ሚካኤል

መልአከ ሰላም ቀሲስ መስፍን (ዶ/ር) እንዲሁም ሌሎች አባቶች እና ከየክፍለ ከተማው የመጡ የሰ/ት/ቤት አባላት በተገኙበት በሠርክ ጸሎት መርሃ ግብሩ ተጀምሯል።

በማስከተልም “ህየንተ አበውኪ ተወልዱ ለኪ ደቂቅ”   

“በአባቶች ፈንታ ልጆች ተወለዱልሽ” መዝ 44፥16

የሚለው ምስባክ ተሰብኮ በማስከተልም በርእሰ ደብር ብርሃኑ አካል

“እነሆ የጠራኸኝ” 1ኛ መ ሳሙ 3፥5

በሚል ኃይለ ቃል ትምህርት አስተላልፈዋል።

የሰ/ት/ቤቱ ሊቀ መንበርም የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክት አስተላልፈዋል።

ላለፉት 3 ዓመታት በመላው ዓለም በተከሰተው ወረርሽኝ ምክንያት ጉባኤውን በአካል ማድረግ ባይቻልም ዘመኑ የፈጠረውን የመገናኛ ዘዴ በመጠቀም ዓመታዊ ጉባኤው ተካሂዷል።

እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ በ2014 ዓ/ም አንድነት ጉባኤው በተመሠረተበት ቤዛ ኩሉ ሰ/ት/ቤት አዘጋጅነት ለሚቀጥሉት 3 ቀናት ጉባኤው የሚቀጥል ሲሆን የዕለቱን ክንውኖች እየተካታተልን የምንዘግብ መሆናችንን እንገልፃለን።